የአባል መብት

ማንኛውም የፓርቲ ሙሉ አባል የሚከተሉት መብቶች ይኖሩታል፡-

  1. በፓርቲው አካላት ምርጫዎች የመምረጥና የመመረጥ፤
  2. በፓርቲው ጉባኤዎች የመሳተፍ፣ በውይይት የመካፈልና በድምፅ በሚወሰኑ ጉዳዮች ላይ ድምፅ የመስጠት፣ በማንኛውም ጉዳይ ላይ በሕጋዊ መድረኮች ሐሳቡን በጽሑፍም ሆነ በቃል የማቅረብ፤
  3. በማንኛውንም የፓርቲ አካል ወይም አባላት ላይ በተቻለ መጠን በመረጃ የተደገፈ ገንቢ ሂስ የማቅረብ፤
  4. በየትኛውም የፓርቲ ውሳኔ ቅር ከተሰኘ ቅሬታውን በመተዳደሪያ ደንቡ መሰረት በየደረጃው ለሚመለከተው አካል የማቅረብ፤
  5. ስለራሱ፣ ስለአካል፣ ስለፓርቲው ማወቅ የሚገባውን ነገር እስከ ፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ የመጠየቅና መልስ የማግኘት፤
  6. የፓርቲውን መተዳደሪያ ደንብ፣ ፕሮግራም፣ አቋሞችና ውሳኔዎች ለሌሎች የማሳወቅ፤ የማስተዋወቅ፤ የማሥረጽና በተጨባጭ እንዲተገበር የማድረግ እና፤
  7. በየትኛውም ጊዜ በጽሑፍ አመልክቶ እና በእጆቹ የሚገኙ የፓርቲው ንብረቶችን ኃላፊነት በተሞላበት አግባብ አስረክቦ ከአባልነት መልቀቅ ይችላል።